Etiopisk Forening i Norge
ክፍል አንድ፤ የስራ አፈላለግ ስልት
  ህ የሥራ አፈላለግ ስልት ውጭ በምንገኝ ኢትዮጵያዊያን ላይ ያተኮረ ቢሆንም የትም አገር ቢሆን ለማንኛውም ዜጋ ይጠቅማል፡፡ ምናልባት በማደግ ላይ ያሉ አገሮች ይህንን የሥራ አሰጣጥና አፈላለግ ስልት እምብዛም አይጠቀሙበት ይሆናል፡፡ በምዕራብያዊያን አገሮች ውስጥ ግን ስልቱ የተለመደ ነው፡፡
Ethiopia addis ababa amharic

ስለዚህ ማንኛውም ዜጋ አገሩ ውስጥም ሆነ ሌላ አገር ቢኖርም፤ እዚህ ጽሁፍ ላይ የተጠቀሰውን የሥራ አፈላለግ ደንብና ስርአት ቢያውቅ እጅግ ይጠቅመዋል፡፡ ይህንን ስልት በተገቢው ከተጠቀሙበት ከአንድ ስራ በላይም ሊያገኙ ስልሚችሉ ስራ መምረጥ ይችላሉ፡፡ ለምሳሌ እኔ ባንድ ወቅት ላይ ሁለት ሥራዎች አግኝቼ አንዱን የተሻለውን ልመርጥ ችያለሁ፡፡

ይህም ሊሆን የቻለው ሥራ ላይ እያለሁ ቢሆንም ሶስት ዓመታት ሙሉ የተሻለ ሥራ ፍለጋ ላይ ስለነበርኩ በራሴ ስህተትና ትምህርት ከወሰድኩ በኋላ ነው፡፡ የመጀመሪያም ሆነ የተሻለ ሥራ ለማግኘት ቋሚ የሆነ ህግና ደንብ የለም፡፡ እንደ ሁኔታው ይለያያል፡፡ በግሌ የማውቀውንና የወሰድኩትን ልምድ ለሌሎች ባካፍል ግን በጣም ደስ ይለኛል፡፡

  ዚህ የኢትዮጵያውያን ማህበር በኖርዌይ መረበ ገጽ ላይ የቀረቡት የስራ አፈላለግ ስልቶች በደንብ ተነበው በተገቢው ከተፈፀሙ አንድ ስራ ማግኘት ቀርቶ ስራ ለመምረጥም ጭምር እድል ያሰፋሉ፡፡ ስልቶቹ የተጻፉት ባንድ ንጋት ምርምር አይደለም፡፡ ስለዚህ እርስዎ ውጤት ለማግኘት ከፈለጉ በስልቶቹ መሰረት ልምምድ፣ ክትትልና ትኩረት ማድረግ አለብዎት፡፡
 ልቱን በቅደም ተከተል አንብበውና ተረድተው በተግባር ከተረጎሙት ስራ የማግኘቱ ዕድል ይሰፋልዎታል!
በነዚያ ሦስት አመታት ውስጥ ከመቶ በላይ ማመልከቻዎች ልኬ ወደ በርካታ ቃለ ምልልሶች ተጠርቼ ነበር፡፡ በደንብ እየታሸሁኝና እየበሸኩኝ ስህተትም ሆነ ትምህርት ወስጃለሁ፡፡ ስለዚህ እርስዎ ስልቱን በተገቢው ካዎቁት ልክ እንደኔ ማንም ወገኛ ስራ ቀጥሪ በነገር አያሸዎትም!!! አሁን ኮተት አታብዛብኝ፥ ይልቅስ ወደ ቁም ነገሩ እንግባ አይሉኝም አንዴ…? በቃ እሺ…


ቅድመ ዝግጅትና ሁኔታዎች፤
  ስደት የምንኖር ኢትዮጵያዊያን የፈለገውንና የተመኘነውን የስራ አይነት በሙያችን ለማግኘት በርካታ መሰናክልቶች ያጋጥሙናል፡፡ በተለይ የመኖሪያ ፈቃድ የሌለን በምንሆን ጊዜ ደህና የሆነ ስራ በሙያችን ለማግኘት ያስቸግራል፡፡ በዚህም ላይ ደግሞ ጸጉረ ልውጦች ስለሆንን ቀጣሪዎች ጥርጣሬ ይገባቸዋል፡፡ ቀጣሪዎች እኛን ስራ ለመስጠት ቢፈልጉም እንኳን ያገሬው ሰራተኞች አይፈልጉ ይሆናል በማለት ከመቀጠር የሚቆጠቡበትም ጊዜ አለ፡፡ አብዛኛው ስራ የሚገኘውም በዝምድና፣ በትውውቅና በጓደኝነት ነው፡፡ እኛ ታዲያ ከፈረንጅ ጋር ዝምድና የለንም፡፡ ትውውቅና ጓደኝነትም ለመፍጠር አጋጣሚው መፈጠር አለበት፡፡ ይህንንም አጋጣሚ እራሳችን ከጊዜ ጋር መፍጠር አለብን፡፡ ስዴት ውስጥ ሆኖ ማንኛውንም ስራ ለማግኘት ወጣ ገባ ከመሆኑም በላይ ውስብስብ ነው፡፡ እያንዳንዳችን ግን ስራ ለማግኘት ተጨማሪ ጥረት ማድረግ አለብን፡፡ ታዲያ ይህንን ወጣ ገባ የሆነ ጉዞ እንዴት እንወጣዋለን? ስራ የማግኘት እድላችንንስ እንዴት ማስፋት እንችላለን?

ያገሩን ባህልና ቋንቋ ከሞላ ጎደል መቻል፣ የህዝቡን ያኗኗርና የአቀራረብ ዘይቤንም በቅጡ ማወቅ ደህና ስራ ለማግኘት ትልቅ አስተዋፅኦ አለው፡፡ ይህንን ማዎቅ ስራ ከማግኘትም ባሻገር በግል ህይወታችንና በሌሎች የማህበራዊ ጉዳዮች ላይም ጭምር በዕውቀት እንዲንዳብር ይረዳናል፡፡

ወደ ክፍት ስራዎች ማስታወቂያ ላይ
-